13

.

"በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው::" የማቴዎስ ወንጌል 7: 4

"እናንተ የተጠማችሁ ሁሉ፥ ወደ ውኃ ኑ፥ ገንዘብም የሌላችሁኑና ግዙ ብሉም ኑ ያለ ገንዘብም ያለ ዋጋም የወይን ጠጅናወተት ግዙ።" ትንቢተ ኢሳይያስ 55 : 1

Friday, September 2, 2011

ሶስቱ ምክሮች


ባንድ ወቅት ባልና ሚስት አብረው ሲኖሩ በማህላቸው ልዩ የሆነ ፍቅር
ነበራቸው፡፡ ሁለት ልጆችም ነበራቸው፡፡ በቤታቸው የሚላስ የሚቀመስ
በመጥፋቱ ይህንን ችግር ለዘለቄታው ለመፍታት ባል ራቅ ብሎ ሊሰራ
ተስማምተው፤ ባል ራቅ ወዳለ ከተማ ሄዶ መስራት ጀመረ፡፡ በተከታታይ ለ
13 ዓመታት ሰራ ከዚያም ወደናፈቁት ቤተሰቦቹ ለመሄድ ተነሳ፡፡
ያልገመተው ነገር ከቀጣሪዎቹ ምን?
ደሞዝ፡ ደሞዙ ምን ሆነ? በተለያየ ምክንያት
ተቆራርጦ ከሚጠብቀው ከግማሽ በታች የሆነውን 3000 (3 ሺ) ተሰጠው፡፡
ምን ያድርግ? ተመልሶ እዛው ስራውን ይቀጥል? ወደ ናፈቁት
ቤተሰቦቹ ይሂድ? ይቻላል ግን ተመልሶ ቢሰራ ደሞዙ መቆራረጡ አይቀሬ
ነው፣ ወደ ቤተሰቦቹ እንዳይሄድ በ13 ዓመት ይህን ብቻ ሰራሁ ቢል ማን
ያምነዋል? ሰለዚህ ሌላ ቦታ ለመስራት ወሰነ ጉዞ ---------------- አንድ አባት
አገኘ --------“ወዴት ትሄዳለህ ልጄ ምንስ ትፈልጋለህ?” አሉት፣ አሱም
ሁሉንም ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው ነገራቸው፡፡ አኝህ አባት አንዲህ
አሉት “እንግዲያውስ የምትፈልገውን ማግኘት ቀላል ነው፡፡” እሱም "እነዴት
አባቴ?" ሲል ጠየቃቸው እሳቸውም "በል አንድ ሺ ብሩን አምጣና
እነግርሀለሁ" አሉት የቸገረው ነውና ነገሩ አሱም አንስቶ አነድ ሺ ብሩን
ይሰጣል እኝህ አባትም "አቆራጭ ነው ብለህ በማታውቀው መንገድ አትሂድ"
ይሉታል፡፡ "ሁለተኛውን ሺ አምጣና ሁለተኛውን መንገድ ልንገርህ" ይሉታል
አሱም በየዋህነት ሁለተኛውን ሺ ይሰጣል ፣ "በማያገባህ አትግባ"
ይሉታል፡፡ "ይህው ነው አባቴ" ቢላቸው "አዎን ልጄ ይልቁኑም 3ኛውን
አምጣና በጣም አስፈላጊውንና የመጨረሻውን ስጦታዬን ልሰጥህ" አሉት፡፡
ሰጠ፡፡ እሳቸውም "ክፉ ለማድረግ አትቸኩል" ብለው "በል ልጄ በቀጥት
ወደ ቤትህ ሂድ" ብለው በባዶ ኪስ ግን ከሱሰት ምክሮች ጋር አሰናበቱት፡፡
እሱም ጉዞውን ወደ ቤቱ አደረገ፡፡ በመንገድ ነጋዴዎች አግኝቶ እያወጋ ሲጎዝ
መሸ ነጋዴዎቹ ለምን ባቆራጭ አንሄድም በማለት ጉዞ ጀመሩ አሱም
አብሯቸው ጉዞ እንደጀመረ የኛ አባት ምክር ትዝ አለው "አቆራጭ ነው ብለህ
በማታውቀው መንገድ አትሂድ" የሚለው ስለዚህ ተመልሶ በሚያውቀው
መንገድ ተጉዞ ብቻውን ከጨለመ ከተማ ገባ፡፡ "የመሸበት አንግዳ ንኝ
አሳድሩኝ" ማለት ጀመረ----------አነድ ሰው ተጠግቶት "የውልህ ወንድሜ አዛ
ሰው ቤት ሂድ ያሳድርሀል ነገር ግን እዛ ሰው ቤት የገባ አይወጣም
ለማንኛውም አድልህን ሞክር" አለው፡፡ አሱም የተባለበት ቤት አንኮክቶ "ቤት
የእንግዳ" ነው ተብሎ ገባ፡፡ ታዲያ ከቤቱ ባለቤት ጋር ሲያወጉ ከየት
እንደመጣ ቢነግረው ባለቤቱ ተገርሞ "አነዴት ሆነህ ተረፍክ? በል" ቢለው ባለ
ፀጋው "ከመኑ?" አለ እንግዳው “ምነው ባልከው መስመር ይመጡ የነበሩ
ነጋዴዎች ተዘርፈው ግማሾቹም ተገለው ዘሬ ከተማው ለቀሶ ብቻኮ ነው፡፡”
ትዝ አለው ያቺ በአንድ ሺ ብር የገዛት ምክር በብር የማትገዛው ሕይወቱን
አተረፈችለት ማለት ነው፡፡ ስለ መሽ የቤቱ አመቤት ምግብ ለእንግዳው
ልታቀርብ ከጎዳ ብቅ አለች "ጥያችሁ ጠፋሁ አደል?" አለች፡፡ እንግዳው
አይኑን ማመን አልቻለም የተወሰነ አካሏ ብቻ ነው ሰው የሚመስለው በዛላይ
ማስፈራቷ ወደ ጎዳ አስክትገባ ናፈቀ "ከዚህች ጋር አነዴት ትኖራለህ?" ብሎ
አስኪጠይቅ፡፡ ወደ ጎዳ ገባች ሊጠይቅ ሲል አነድ ነገር ትዝ አለው የኛ አባት
ምክር "በማያገባህ አትግባ" የሚለው፡፡ ሆዱ መጠየቅ አየፈለግ ፍላጎቱን
ተቐቌሞ አደረ ፡፡ ደግሞ ሌላ ፈተና የቤቱ ባለቤት ከመሄድህ በፊት የማሳይህ
ነገር አለኝ ብሎ ወደ ጓሮ ወሰደውና የሰው አፅም የሞላበት ሜዳ አሳየው
አንግዳውም "ይሄ ደሞ ምንድነው?" ማለት ፈልጎ ነበር ግን በማያገባህ አትግባ
ብሎ ራሱን፤ራሱን አየነቀነቀ ዝም አለ፡፡ የቤቱባለቤትም ተገርሞ እንዲህ
አለው "በእውነት አንተ የምትገርም ሰው ነህ ይህ የምታየው ሁሉ ስለ ሚሰቴ
የማየገባቸውን አስተያየት ስለ ሰጡ የተገደሉ እንዳነተ አዚህ ቤት በእንግድነት
የመጡ ነበሩ፡፡ አነተ ግን ታላቅ ሰው ሰለሆንክ የሀብቴን ¼ ሰጥቼሀለሁና ይዘህ
ትሄዳለህ" ተብሎ ባለ ብዙ ሀብት ሆኖ ወደ ቤቱ ሄደ፡፡
እዛች ደሳሳ ጎጀ የደረሰው ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት ነበር፡፡ ሁሉም ነገር
ቢለወጥም ቤቱን ግን አላጣውም በትልቅ አንጨት የምትዘጋ
(የምትደገፍ) በሩን ገፋ ሲያደርጋት ተከፈተች፡፡ አይኑ ግን ከማያምነው
ነገር ላይ አረፈ ሚስቱ ሁለት ጎረምሶች ማህል ተኝታለች ጎነበስ ሲል
ጎራዴውን አየ አነሳው አነገታቸውነ ሊቆርጠው በንዴት ጦፎ
እጁን ወደ ላላላላላላላለይይይይይ አነሳ-----------3ተኛው ምክር ትዝ
አለው "ክፉ ለማድረግ አትቸኩል" የሚለው፡፡
ከቤቱ ውጪ በተጋደመው ዛፍ ላይ ቁጭ አለ በተቀመጠበት አነቅልፍ
ይዞት ሄደ፡፡ ነጋ ሚሰት በጠዋት ተነስታ ደፋ ቀና ስትል ድንገት
ባሏን አየችው አልልታዋን አቀለጠችው-----ዘላ ተጠመጠመችበት
ከአንቅልፍ የነቃው ባል በመደናገጥ ስሜት ሳለ አጆቹን ይዛ
ወደቤት ገብታ ሁለቱን ጎረምሶች አስተዋወቀች ""ይህ
የመጀመሪያ ልጅህ ይህ ደሞ ሁለተኛው""" ብላ፡፡ እነግዲህ
የመጨረሻው ምክር የልጆቹን ነፍስ ከማጠፋት ረዳው ማለት ነው፡፡
ሁላችሁም አስቲ ራሳችሁነ ጠይቁ ይህ ሰው ያለነዚህ ምክሮች ቢመጣ ምን
ይፈጠር ነበር?
የሚያስተምረን ነገር ካለ ምን ያስተምረናል አናንተ ምን ተማራችሁበት?
አንድ አኔ የተማርኩበትን ልጥቀስላችሁ
እኔ ይህ ነገር ትዝ ባለኝ ቁጥር የሚያስታውሰኝ በትንቢተ ኤርምያስ ም6
ቁ16 ላይ "በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱም፤ የቀደመችውን መንገድ
ጠይቁ፤ መልካሚቱን መንገድ ወዴት አነደሆነች ጠይቁ፤ በእርሷም ላይ ሂዱ
ለነፍሳችሁም መድሀኒት ታገኛላችሁ፤ እነርሱ ግን "አንሄድባትም" አሉ፡፡"
ካንድ ቦታ የሚያደርሱ የሚመስሉ ብዙ መንገዶች ሊኖሮ ይችላሉ፤ ሐዋርያው
"ቅን የምትመስል መንገድ አለች" እነዳለው፡፡ አንዳንዶች መፆም ሲከብዳቸው
አቆራጭ መንገድ ይፈልጋሉ ከዚያም ጌታ ፆሞልኛል ይላሉ፤ አነዚህን ሰዎች
ግን አንድም ቀን ጌታ በልቶልኛልና አልበላም ብለው አያውቁም፡፡
አነዳንዴም ስታናግሯቸው አኛ ጌታን ምሰሉ ነው የተባልንው ይላሉ ታዲያ
ጌታን መምሰል እንዲህ ነው? መልሱን ለናንተ
ትቼዋለሁ፡፡
እንደ ይሁዳ ወደ ገነት ለመግባት አቐራጭ መንገድ መፈለጉ ብልጣ ብልጥ
ለመሆን መሞከሩ መጨረሻው ሞት ስለሚሆን በመጽሐፍ የተፃፈውን ተምሮ
ጠይቆ ተረድቶ በቀደመችው መንገድ መጎዝ እንጂ አቐራጭ መፈለጉ
አያዋጣም፡፡ "የዋሃን ብፁዓን ናቸው፤ ምድርን የወርሳሉና" አንዲል ማቴ 5:-5
የተባልንውም እንደ እባብ ልባሞች እንደ ርግብ የዋሆች ሁኑ ነው፡፡ ሰፊ ነገር
ብል ደስ ባለኝ፤ ሁላችሁም በየራሳችሁ የምትሰጡትን አስተያየት ለመስማት
ዝግጁ ነኝ፡፡ ሁለት እውነት የለም፤ ያለው አነድ አውነት ብቻ ነው፡፡
"---------------- ሃይማኖት አንዲት ናት፤ ጥምቀትም አነዲት ናት---------"
ኤፌ 4:-4 አምላከ ቅዱሳን ይጠብቀን!

Source:

Tewahido Communion

1 comment: