13

.

"በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው::" የማቴዎስ ወንጌል 7: 4

"እናንተ የተጠማችሁ ሁሉ፥ ወደ ውኃ ኑ፥ ገንዘብም የሌላችሁኑና ግዙ ብሉም ኑ ያለ ገንዘብም ያለ ዋጋም የወይን ጠጅናወተት ግዙ።" ትንቢተ ኢሳይያስ 55 : 1

Saturday, September 3, 2011

አዕማደ ምሥጢራት!


አዕማድ ቋሚ ፣ ተሸካሚ ፣ ምሰሶ ማለት ነው፡፡ ቤተክርስቲያንም የእምነት መሠረት የሆኑትን ትምህርቶች አዕማደ ምሥጢራት ትላቸዋለች፡፡ አዕማድ የተባሉት ልቦናን ከኑፋቄ ፣ ከጥርጥር የሚያድኑ ስለሆነ ነው፡፡ ምሰሶ የሌለው ቤት እንደሚወድቅ ሁሉ አዕማደ ምሥጢራትም ያላመነ ፣ ያላወቀ ሰው ቢኖር ይወድቃል፡፡

አዕማደ ምሥጢራት አምስት ናቸው፡፡ እነዚህም

  1. ምሥጢረ ሥላሴ
  2. ምሥጢረ ሥጋዌ
  3. ምሥጢረ ጥምቀት
  4. ምሥጢረ ቁርባን
  5. ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን ናቸው፡፡

ምሥጢር መባላቸው ስለምንድን ነው

 ምሥጢር
አመሠጠረ ከሚለው ግስ የተገኘ ቃል ሲሆን ስውር ፣ ድብቅ ፣ ሽሽግ ማለት ሲሆን አምስቱ አዕማደ ምሥጢራትም ምሥጢር የተባሉበት ምክንያት
  • በሥጋው ጥበብ ምርምር መረዳት ስለማይቻሉ
  • ላመኑት እንጂ ላላመኑት ሰዎች የተሰወሩ በመሆኑ


ምሥጢር በሁለት ይከፈላል፡፡ እነርሱም፡-

የፈጣሪ ምሥጢር፡- ሊገለጥ የማይችል ነው፡፡ ከ እስከ የሌለው ምሥጢርም ይባላል፡፡

የፍጡራን ምሥጢር፡- በጊዜ የሚገለጥ /የሚታወቅ/ ነው፡፡ የሰውና የመላእክት ምሥጢር በዚህ ውስጥ የሚካተት ነው፡፡
ምሥጢረ ሥላሴ
ሥላሴ፡- የግእዝ ቃል ሲሆን ሦስትነት ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔር አንድ ሲሆን ሦስት ፣ ሦስት ሲሆ አንድ ነው፡፡ ይህ የእግዚአብሔር ሦስትነት ልዩ ሦስት ነው፡፡ ሦስት ብቻ ተብሎ አይቆምምና ሦስት ሲሆን አንድም ነው፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔር የአንድነት የሦስትነት ባለቤት በመሆኑ ሥላሴ ይባላል፡፡

የእግዚአብሔር አንድነት

እግዚአብሔር አንድ ነው ስንል በመለኮት ፣ በባሕርይ ፣ በአገዛዝ ፣  በሥልጣን ፣ በሕላዌ /ሕልውና/ በመፍጠር በልብ በቃል በእስትንፋስ ይህን ዓለም በመፍጠር እና በማሳለፍ ይህን በመሳሰለው ነው፡፡

  በመፍጠር መዝ 101፡25 ፣ ዘፍ 1፡1 ፣ ኢሳ 66፡1-2 
  በሥልጣን ዮሐ 10፡30 
  በመለኮት መለኮት ማልኩት ከሚለው የዕብራይስጥ ቃል የተገኘ ሲሆን መንግስት ግዛት ማለት ነው፡፡ ይህም ለእግዚአብሔር ብቻ የተሰጠ ነው፡፡ ቆላ 2፡9፣ 1ኛ ጴጥ 1፡3 
  በሕላዌ /ሕልውና/  አኗኗር ማለት ነው፡፡ መብለጥ ፣ መቅደም ፣ መቀዳደም የለባቸውም፡፡ ዮሐ 1፡1-2፣ ዮሐ 14፡10 

የእግዚአብሔር ልዩ ሦስትነት

እግዚአብሔር በስም፣ በአካል፣ በግብር ሦስት ነው፡፡

የስም ሦስትነት አብ ወልድ መንፈስቅዱስ ናቸው፡፡ ማቴ 28፡19፡፡
  እግዚአብሔር አብ፡- ከዘለዓለም እስከዘለዓለም ከሦስቱ አካላት የአንዱ የአብ ስም ነው፡፡ 1ኛ ጴጥ 1፡2፣ ዮሐ 3፡16
  እግዚአብሔር ወልድ፡- ከዘለዓለም እስከዘለዓለም ከሦስቱ አካላት የአንዱ የወልድ ስም ነው፡፡ ወልድ ሰው በሆነ ጊዜ በተለያ ስሞች ተጠርቷል፡፡ እነዚህም፡-
  ኢየሱስ- መድኃኒት አዳኝ ማለት ነው፡፡ ማቴ 1፡21
  ክርስቶስ- መስሕ /ንጉሥ/ ማለት ነው፡፡ ሉቃ 2፡11፣ ዮሐ 4፡25
  አማኑኤል-እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው ማለት ነው፡፡ ትን.ኢሳ 7፡14 ፣   ማቴ 1፡21



እግዚአብሔር ወልድ አምላክ ስለመሆኑ ማስረጃ

ዮሐ 20፡9 ፣ ሮሜ 10፡12 ፣ ዮሐ 1፡1 ፣ ዮሐ 1፡14 ፣ ዮሐ 20፡28 ፣ ዮሐ 4፡42 ፣ የሐዋ.ሥራ 20፡28 ፣ ራዕይ 1፡8 ፣ ትን.ኢሳ 9፡6 ፣ ራዕይ 22፡12 ፡፡

   እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ፡- ከዘለዓም እስከ ዘለዓለም ከሦስቱ አካላት የአንዱ መንፈስ ቅዱስ ስሙ ነው፡፡

መንፈስ ቅዱስ በተለያዩ ስሞች ይጠራል፡፡
  • መንፈስ- ዮሐ 3፡5 ፣ 1ኛ ቆሮ 12፡4 ፣ ዘፍ 1፡2 ፣ ትን.ኢሳ 48፡16
  • የእግዚአብሔር መንፈስ - ት.ኢሳ 61፡6
  • ጰራቅልጦስ /አጽናኝ/ እየተባለ ይጠራል፡፡ ዮሐ 15፡26 ፣ ዮሐ 14፡16 ፣ ዮሐ 16፡7
  • የእውነት መንፈስ፡፡ ዮሐ 15፡26

በአጠቃላይ ሥላሴ በስም ሦስትነት ቢኖራቸውም አንዱ በአንዱ ስም ሊጠራ አይችልም፡፡
የአካል ሦስትነት
    ለአብ ፍጹም ገጽ ፣ ፍጹም መልክ ፣ ፍጹም አካል አለው፡፡
    ለወልድም ፍጹም ገጽ ፣ ፍጹም መልክ ፣ ፍጹም አካል አለው፡፡
    ለመንፈስ ቅዱስም ፍጹም ገጽ ፣ ፍጹም መልክ ፣ ፍጹም አካል አለው፡፡
የግብር ሦስትነት
የአብ ግብሩ መውለድ ማስረጽ ፣ የወልድ ግብሩ መወለድ ፣ የመንፈስ ቅዱስ ግብሩ መስረጽ ነው፡፡ አብ ወልድን ውልዷል ፤ መንፈስ ቅዱስን አስርጽዋል ፤ መንፈስ ቅዱስ ሰርጽዋል፡፡ ወልድ ተወልዷል ፤ መንፈስ ቅዱስ ሰርጽዋል፡፡

  • አብ ወልድን ወለደ ማለት ፤ ከአካሉ ከባሕርይው ፤ አስገኘው ማለት ነው፡፡
ምሳሌ የሰው ነፍስ ልብነቷ /አሳቢነቷ/ ቃልነቷን እንደሚያስገኘው
  • ወልድ ከአብ ተወለደ ማለት ፤ አብን አክሎ አብን መስሎ ከአብ ተገኘ ማለት ነው፡፡
ምሳሌ የነፍስ ቃልነቷ ከልብ እንደተገኘ
  • አብ መንፈስ ቅዱስን አሰረጸው ማለት ፤ ከአካሉ ከባሕርይው አስገኘው ማለት ነው፡፡
ምሳሌ የነፍስ ልብነቷ እስትንፋስነት /ሕይወትነቷን/ እንዳስገኘ ማለት ነው
  • መንፈስ ቅዱስ ከአብ ሰረጸማለት ፤ አብን አህሎ አብን መስሎ ከአብ ተገኘ ማለት ነው፡፡
ምሳሌ የነፍስ እስትንፋስነቷ ከልብ እንደተገኘ

ለምሥጢረ ሥላሴ የፍጡራን ማስረጃ


የሰው ነፍስ፡- የመናገር ፣ የማሰብ ፣የመተንፈስ /የሕያውነት/ ሁኔታ አላት፡፡ ማሰብ በአብ ፤ መናገር በወልድ ፤ ሕያውነት በመንፈስ ቅዱስ ይመሰላሉ፡፡ የነፍስ ልብነቷ ቃልነቷን ሕይወትነቷን ከራሷ ታስገኛለች፡፡ ነፍስ ስትገኝ በሦስትነቷ በአንድ ጊዜ ተገኘች እንጂ ልብነቷ ቀድሞ ቃልነቷ እስትንፋስነቷ በኋላ አልተገኘም፡፡ ነፍስ በኩነታት ሦስትነት ቢኖራትም በአካል አንድ ናት፤ ሥላሴ ግን አብ አካላዊ ልብ፤ ወልድ አካላዊ ቃል ፤ መንፈስ ቅዱስ አካላዊ እስትንፋስ ነው፡፡

ፀሐይ፡- አንድ ስትሆን ሦስትነት አላት፡፡ አካሏ ፣ ብርሃኗ ፣  ሙቀቷ ናቸው፡፡ አካሏ በአብ፣ ብርሃኗ በወልድ፣ ሙቀቷ በመንፈስ ቅዱስ ይመስላል፡፡

ባሕር፡- ስፋቱ በአብ፣ ርጥበቱ በወልድ ፣ ማዕበሉ በመንፈስ ቅዱስ ይመሰላል፡፡

ስለ ምሥጢረ ሥላሴ የማገናዘቢያ ጥቅሶች

            በብሉይ ኪዳን     
ት.ኢሳ 48፡12 ፣ መዝ 117፡16፣ ዘኁ 6፡24 ፣ ዘፍ 3፡22 ፣ት.ኢሳ 6፡3 

            በሐዲስ ኪዳን
1ኛ ቆሮ 19፡14 ፣ ማቴ 17፡15 ፣ ሉቃ3፡22 ፣ ማቴ 28፡19 ፣ ማቴ 3፡16 ፣ ዩሐ 16፡7 ፣ የሐዋ.ሥራ 7፡55 ፣ ዮሐ 14፡15 ፣ ራዕይ 14፡1-2

ምሥጢረ ሥጋዌ

ሥጋዌ ‹‹ተሰገወ›› ከሚለው የግዕዝ ግስ የወጣ ሲሆን ሥጋን መንሳት /ሰው መሆን/ ማለት ነው፡ ምሥጢረ ሥጋዌ ከሦስቱ አካላት አንዱ እግኢአብሔር ወልድ ሰው የመሆኑ ምሥጢር ነው፡፡ ሰው ሆነ ማለትም የሰውን ባሕርያት ነፍስና ሥጋን በረቂቅ ባሕርይው ተዋሐደ ማለት ነው፡፡

አምላክ ለምን ሰው ሆነ?

 - እግዚአብሔር አዳምና ሔዋንን ለማዳን ቃል ኪዳን ስለገባላቸው ቃል ኪዳኑን ለመጠበቅ አምላክ ሰው ሆነ፡፡ ዘፍ 2፡17 ፣ 1ኛ ተሰ 5፡9 ፣ ገላ 4፡4፡፡ በስመጨረሻ ሁሉን አሟልቶ በአርአያውና በምሳሌው ለፈጠረው ሰው ፍጽም የሆነ ፍቅሩን በገሀድ ለማሳየት አምላክ ሰው ሆነ፡፡ ዮሐ 3፡6
 - ምድር ለመልካም ተፈጥራ ሳለ ስለሰው ኃጢአት በመረገሟ በቅዱሳን እግሮቹ ተራምዶ ሊቀድሳት በደሙ ፈሳሽነት ሊያነጻት አምላክ ሰው ሆነ፡፡ ት.ኢሳ 45፡18 ፣ ዘፍ 3፡17 ፡፡
 - ሰው በምድር ካለ የሚቀናቀነው የለም ስለሆነም በልብ መታበይ አምላክ ነኝ እንዳይል ሁሉን የፈጠረ አምላክ መኖሩን ሊያስረዳ፡፡
   ዲያብሎስ አዳም ሔዋንን ከይሲ / እባብ/ ሰውነት አድሮ እንዳሳታቸቸው እርሱም በሰው አካል አድሮ ሊያድናቸው፡፡

አምላክ ሰው ባይሆን ማዳን አይችልም ነበረን?

      ፍርድ እንዲገባ

-  አምላካችን ሁሉን ማድረግ የሚችል የማይሳነው ነው፡፡ ዘፍ 18፡14 ፣ ኢዮ 39፡4
ሉቃ 1፡37 ነገር ግን ሥርዓት አልባ አይደለም ፤ ሁሉን በሥርዓት ያደርጋል፡፡ 1ኛ ቆሮ 14፡33
-  የፍርድ ቃልን የሚለውጥ አይደለምና በመሐሪነቱ አንጻር ግን ይቅር ባይ ነው፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔር ትክክለኛና የማይሻር ዳኝነቱን ሊያሳይ ሰው ሆነ፡፡
ዕብ 6፡17፣ ማቴ 7፡7 ያዕ 2፡5

   ፍጹም ፍቅሩን ሊያስረዳን


-  የበደለ ኃጢአትን የሠራ ሰው ነው፡፡ በእግዚአብሔር ጥተኛ ፍርድ መሠረት የኃጢአትን ዋጋ መክፈል ያለበት ሰው ነው፡፡ ነገር ግን ከሰው ልጆች መካከል ባሕርይው ያላደፈበት ወንጀለኛ ያልሆ ስለጠፋ ሁሉም ራሱ መዳ የሚያስፈልገው ስለሆነ ፍጡር ሰው ፍጡር ሰዎችን ማዳን አልቻለም፡፡ ስለዚህ የማይለወጥ አምላክ ለተሠራው በደል የሚከፍል ሞትን ይፈጽም ዘንድ ሰው ሆነ፡፡ ከአመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደ፡፡ ት.ኢሳ 59፡16 ፣ ሮሜ 3፡23
ሮሜ 5፡6


የአምላክ ሰው መሆን /መወለድ/

ከቅድስት ድንግል ማርያም ሲወለድ ማኅተመ ድግልናዋ ሳይለወጥ ነው፡፡ በዚህ ድግል ስትባል ትኖራለች፡፡ ምሳሌው አምላክ ሰውም ሲባል መኖሩ ነው፡፡ በሌላ በኩል ከድንግል ማርያም ያለ ዘር ሩካቤ መወለዱ ለአካላዊ መሲህ መለያ ምልክቱ ነው፡፡ ሕጻናትን በማሕጸን የሚፈጥር የእግዚአብሔር ልጅ በሥጋና በነፍስ በሕጻናት ጽንስ መጠን በድንግል ማርያም ማሕፀን ተጸነሰ፡፡

ጌታ ከጽንስ ጀምሮ የሰውነት ጠባዩ አልተለወጠም፡፡ 9ወር ከ5 ቀን ሲሆ ተወለደ፡፡ በልደቱም እናቱ ጭንቅ ምት አላገኛትም፡፡ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አምላክን በድንግልና መውለድ ከሌሎች ሴቶች ፀንሶ መውለድ ይለያል፡፡ 

Source:
Kidane Mhret blog

No comments:

Post a Comment