13

.

"በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው::" የማቴዎስ ወንጌል 7: 4

"እናንተ የተጠማችሁ ሁሉ፥ ወደ ውኃ ኑ፥ ገንዘብም የሌላችሁኑና ግዙ ብሉም ኑ ያለ ገንዘብም ያለ ዋጋም የወይን ጠጅናወተት ግዙ።" ትንቢተ ኢሳይያስ 55 : 1

Saturday, September 3, 2011

የቤተክርስቲያን ታሪክ


እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፡- በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱም  የቀደመውንም መንገድ ጠይቁ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደሆነች ዕወቁ በእሷም ላይ ሂዱ ለነፍሳችሁ እረፍትን ታገኛላችሁ፡፡ ኤር6፡16
 የቤተክርስቲያን ታሪክ ትርጉም
የቤተክርስቲያን ታሪክ ማለት የክርስትና ዕምነት ታሪክ ማለት ነው፡፡ በቤተክርስቲያን ታሪክ የክርስትና ዕምነት የአምላክ መገለጥ ነው፡፡ ይሁን እንጂ በዘመንና በቦታ የተደረገ ስለሆነ መቼ፣ እንዴት እንደሆነ የምናውቅበትና በጉዞው ሁሉ የገጠሙትን ችግሮችና የምንማርበት ነው፡፡
 
የቤተክርስቲያን ታሪክ ጥቅም
የቤተክርስቲያን ታሪክ የዓለም ታሪክ አንዱን ክፍል ይዞ ስለሚገኝ የሕዝቦችን የሥልጣኔ እርምጃና ታሪክ ለማጥናት ለሚፈልግ ሰው ጠቃሚ መረጃ ይሰጣል፡፡
አንድም ምዕመን የቤተክርስቲያን ታሪክን ለማጥናት በሚፈልግበት ጊዜ

-    የዕምነቱን ታሪክ ለማወቅ
-    አባቶች በየጊዜው ስላስተማሩበት የትምህርት የሕዝብ ፀባይ እንዴት እንደተሻሻለ ለማወቅና ለማነጽ
-    የቤተክርስቲያንን ከፍተኛነትንና ጠቃሚነት ለመገንዘብና ራሱንም በእምነት ለማጽናት ከፍተኛ ጥቅም አለው፡፡

የቤተክርስቲያን ታሪክ ጥናት ምንጮች
የቤተክርስቲያንን ታሪክ በዝርዝር ለማጥናት ለሚፈልግ ሰው
-    በብሉይ ኪዳንና ሐዲስ /መጽሐፍ ቅዱስ/ እና የትርጓሜ መጽሐፍት፣
-    የቤተክርስቲያን ታሪክ አባቶች የጻፏቸው መጻሕፍት / በየጊዜው በተደረጉ ጉባዔዎች የተወሰኑትንና ነገሥታት ለቤተክርስቲያን የደነገግናቸው ሕጎች
-    ታሪኩ በተፈጸመበት ቦታ ተገኝተውና ታሪኩ በተፈጸመበት ዘመን የኖሩ የቤተክርስቲያን የውጭ ታሪክ ጸሐፊዎች የጻፏቸው መጻሕፍት
-    በየጊዜው የተገኙ የክርስቲያናት መቃብራት፣ መቅደሶች፣ ስዕሎች፣ ገንዘቦች፣ ጽሑፎችና እነዚህን የመሳሰሉት ቅርጾች /ለማገናዘብያነት የሚረዱ/
የቤተክርስቲያን  ትውፊታዊ መረጃዎች ያስፈልጉታል፡፡

የቤተክርስቲያን ዘይቤያዊ ፍቺ
1)  ‹‹ቤተ ክርስቲያን›› የግእዝ ቃል ሲሆን በአማርኛ እንጠቀምበታለን፡፡ ፍቺውም የክርስቲያኖች ቤት የክርስቲያኖች መኖርያ ማለት ነው፡፡ በዚህ ቀጥተኛ አፈታት መሠረት ሕፃኑ፣ ሽማግሌው፣ ወንዱ፣ ሴቱ፣ሁሉም በአንድ ላይ ተሰብስበው ጸሎት የሚያደርስበት የጌታችን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደሙ የሚፈተትበት ቅዱስ ቦታ /ሕንፃ ቤተክርስቲያንን/ ያመላክታል፡፡ የሐዋ 20፡28፣ 1ኛጢሞ3፡15፣ 1ኛ ነገ9፡3

2)  ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የባህርይ አምላክ የዓለም መድኃኒት መሆኑን የሚያምኑ ሰዎች ሁሉ ቤተክርስቲያን ይባላሉ፡፡የያዕቆብ የእስራኤል ወገን የሆኑ በሙሉ ቤተእስራኤል እንደሚባሉ በክርስቶስ ክርስቲያን የሆኑ የክርስቲያን ወገኖችም ቤተክርስቲያን ይባላሉ፡፡ ሐዋ5፡11፣ የሐዋ12፡1፣ 1ኛ ቆሮ3፡16፣ 2ኛ ቆሮ6፡16፣ ዮሐ14፡23፣ የሐዋ 9፡3

3)  የክርስቲያኖችም ማኅበር ፣ የክርስቲኖች ጉባዔ ፣ የክርስቲያኖች ስብስብ /አንድነት/ ቤተክርስቲያን ይባላል፡፡ ሮሜ16፡1፣ 1ኛጴጥ5፡13

የቤተክርስቲያን ዕድሜ 
አንዳንድ የቤተክርስቲያን ሊቃውንት ቤተክርስቲያን የሚለው ቃል በምሥጢራዊ አፈታት ሲፈቱ ቤተክርስቲያን ማለት እግዚአብሔር ከሰውና ከመላእክት ጋር ያለው ግንኙነት ነው ይላሉ፡፡ በዚህም መሠረት የቤተክርስቲያን ዕድሜ በሦስት ይከፍሉታል፡፡
1. ሰው ከመፈጠሩ በፊት በዓለመ መላእክት የነበረች የቅዱሳን መላእክት አንድነት፤
2. በዘመነ ብሉይ የነበሩ ደጋግ አባቶች ከእግዚአብሔር ጋር የነበራቸው ግንኙነት፤
3. በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ደም የተመሠረተችውና በመንፈስ ቅዱስ የምትመራው ዓማናዊት ቤተክርስቲያን /የምዕመናን አንድነት / እሷም የፀጋና የፅድቅም ምንጭ ናት፡፡ ኤፌ3፡9
እነዚህ የቤተክርስቲያን ዕድሜዎች በዝርዝር ስንመለከታቸው

1)  ዓለመ መላእክት እግዚአብሔር መላእክትን በከተማ በነገድ መቶ አድርጎ ከፈጠራቸው በኋላ ተሰወረባቸው፤ እነርሱም ፈጣሪያቸን ማን ይሆን እያሉ ይጠይቁ ጀመር በዚህ ጊዜ በክብር ከፍ ብሎ ይገኝ የነበረው ሳጥናኤል ‹‹እኔ ፈጠርኳችሁ›› በማለቱ ክርክር ተነስቶ መላእክት ለሁለት ተከፈሉ፡፡ በመጨረሻም ሳጥናኤልና ሠራዊቱን ወደ ዘላለም ፍርድ፣ ባሉበት የጸኑትን ቅዱሳን መላእክት ደግሞ የዘላለም ህይወትና ክብር ተሰጣቸው፡፡ በዚህም መላእክት ከእግዚአብሔር ጋር ግንኙነት ጀመሩ፡፡ ራዕ12፡28፣ ኢሳ14፡15

2)  በብሉይ ዘመን የነበሩ ደጋግ አባቶች

በአራት ይከፈላሉ፡፡ እነሱም

1. ዘመነ አበው            3. ዘመነ ነገሥታት  
2. ዘመነ መሣፍንት        4. ዘመነ ነብያት /ካህናት/ ናቸው፡፡
የቤተክርስቲያን ታሪክ ከአዳም እስከ ክርስቶስ እርገት 5500 ቅድመ ልደተ ክርስቶስ 34 ዓመተ ምህረት ነው፡፡ /ከፍጥረተ ዓለም እስከ ጰራቅሊጦስ/

ምንጭ ፡- የ/መ/ገ/ጽ/ቅ/ጊ/ቤ/ክ/ሰ/ት/ቤት

No comments:

Post a Comment