13

.

"በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው::" የማቴዎስ ወንጌል 7: 4

"እናንተ የተጠማችሁ ሁሉ፥ ወደ ውኃ ኑ፥ ገንዘብም የሌላችሁኑና ግዙ ብሉም ኑ ያለ ገንዘብም ያለ ዋጋም የወይን ጠጅናወተት ግዙ።" ትንቢተ ኢሳይያስ 55 : 1

Friday, September 2, 2011

አርጋኖን ዘሃሙስ : ምዕራፍ 1

በዕብራይስጥ ማሪሃም የተባልሽ የተመረጽሽ ድንግል እመቤቴ ማርያም ሆይ መላእክትን ለፈጠረ በኪሩቤል ላይ ለሚቀመጥ እናቱ ለምኝልኝ፡፡፪. ከሚያሰጥም ባሕር ማዕበልም ሞገድ፡፡ ከከበደ ዓለም ኅልፈት ጥፋት በጸሎትሽ አድኝኝ፡፡፫. አምላክን የወለድሽ ድንግል ሆይ በላዬ ያደረውን የኃጢአቴን ሽታ አርቂው፡፡ በጸሎትሽም መዓዛእንደ ኪሩቤል ዕጣን ሽታ እንደ ሱራፌልም ጽንሐሕ ጸሎቴ ደግሞ ያማረ የተወደደ እግዚአብሔርምየተቀበለው ይሁን፡፡፬. ምስጋናን የተመላሽ ድንግል ሆይ እንዳልወድቅ ከመሰናክል አድኝኝ ደግፊኝ፡፡ ጥልቅቅ የሚያደርግአእምሮ የሚያሰጥ ወይን መጠጥን እንደጠጣ ልቤ ዕውቀት አጥቷልና፡፡፭. ሕጉን ትእዛዙን ለመጠበቅ እያሰብሁ ሌሊቱን ሁሉ እደክማለሁ፡፡ ጥቂትም ቆይቶ አናዋዋርየሚለውጥ ሐሳብ ይመጣብኛል፡፡ የዚህን ዓለም ማሠሪያ ከኔ ቁረጭው ሰውነቴ በርሱ ገመድ ተይዟልናለርሱም ከገዛት ነጻ አድርጊኝ፡፡፮. ጸጋ ክብርን የተመላሽ ድንግል ሆይ ከመግፋት ከመገፋት አድኝኝ፡፡ ቅድስና የተመላሽ ድንግል ሆይከመበደል ሌላውንም ከመበደል አድኝኝ፡፡ ከደም አፍሳሽ አድኝኝ፡፡ እኔም ደግሞ የሌላውን ደምከማፍሰስ ሠውሪኝ፡፡፯. የተድላ መፍሰሻ ድንግል ሆይ ከሽንገላ አድኝኝ፡፡ ከሸንጋይም ደግሞ ሠውሪኝ፡፡ የምስጋና መፍሰሻድንግል ሆይ ከሽሙጥ ከስድብ ከሚያስሽሟጥጥና ከሚሰድብ ደግሞ ሠውሪኝ፡፡ተድላ መፍሰሻ ድንግል ሆይ ከሽንገላ አድኝኝ፡፡ ከሸንጋይም ደግሞ ሠውሪኝ፡፡ የምስጋና መፍሰሻድንግል ሆይ ከሽሙጥ ከስድብ ከሚያስሽሟጥጥና ከሚሰድብ ደግሞ ሠውሪኝ፡፡፰. የባለ ጸግነትና የክብር መፍሰሻ ድንግል ሆይ ሰውን ከሰው ከማጣላት አድኝኝ፡፡ ሰውን ከሰውከሚያጣላ ሐሰተኛ ደግሞ ሰውሪኝ የሕይወት የመድኃኒት ምንጭ ሆይ ከቂምና ከቅናት አድኝኝ ከቂመኛከቀናተኛ ደግሞ አድኝኝ፡፡፱. የፈውስ መቅጃ የበረከት አዘቅት ድንግል ሆይ ከፀብ ከክርክር አድኝኝ፡፡ ከሚጣላና ከሚከራከርአድኝኝ፡፡ እሳት የሚለብሱ ኪሩቤልና ሱራፌል በመብረቅ ክንፍ የሚጋርዱሽ የንጉሠ ነገሥት ማደሪያየምትሆን የብርሃን ድንኳን ሆይ፡፡ በሕይወት በመድኃኒት ጋሻ ጋርጅኝ ከአጋንንት ፍላፃ እንድድን፡፡፲. ይቅር ባይ በሆነ ልጅሽም መጋረጃ ሸፍኝኝ፡፡ ሰወን ከሰው ማጣላትን ከተመላ ከመላስ ነገርእንድሠወር አጥሯ ቅጥሯ የማይፈርስ መሠረቷ የማይናወጽ ለዘለዓለም ጸንታ የምትኖር አዳራሽ ሆይ፡፡የመሃይምናን መኖሪያ ወደሚሆን ዕድል ፈንታዬን ጽዋ ተርታዬን ገነት መንግሥተ ሰማያትንአድርጊልኝ፡፡፲፩. ድንግልና አበባን በቅድስናም የበረከት ፍሬን ያፈራች የወይን ቦታ ሆይ፡፡ ንስሐ ፍሬን እንዳፈራንጹሑንም መሥዋዕት እጅ መንሻ አድርጌ ለልጅሽ እንዳቀርብ አድርጊልኝ ለበጎ ሥራም የዋህ ልቡናትሑት ሰብና ስጭኝ፡፡፲፪. ከምድር እስከ ሰማይ የትምደርስ የወርቅ መሰላል ሆይ የመለኮት አንድነት ሦስትነት ወዳለበት፡፡ምሕረት ምንጭ ወደሚቀዳበት ጸሎቴን አሳርጊልኝ፡፡ ጽዋ ተርታዬን ዕድል ፈንታዬንም ይቅር መባልአድርጊልኝ፡፡ ነገር ግን በፍርድ አይደለም ባንቺ በረከት በማቸነፍ ነው እንጂ፡፡፲፫. የልዑል እግዚአብሔር የበኩር ልጁ የጌትነቱ መሣሪያ የብርሃን መጋረጃ ድንግል ሆይ ከክፉ ዕለትከጥፋት ሰዓት በቀን ከሚወረወር ጦር በጨለማም ሌሊት ከሚመላለስ ነገር ሠውሪኝ፡፡፲፬. ከዓውሎ ነፋሰ የተነሣ ምዕመናንን የምታሻግር የመድኃኒት ድልድይ የድኅነት መርከብ ሆይከኃጢአት ማዕበል ሞገድ አሻግሪኝ መርከብ ሰውነቴን እንዳያነዋውፀው፡፡፲፭. የንጹሓን የደናግል መመኪያቸው ንጽሕት ድንግል ሆይ ከኃጢአት ርኩሰት ከማመንዘርም መተዳደፍንጹሕ አድርጊኝ የቅዱሳን ሁሉ መመኪያቸው ቅድስት ድንግል ሆይ በልጅሽ ደም ንጹሕ አድርጊኝ፡፡በበህር ልጅኝ በጎኑ ፈሳሽ የጸዳሁ አድርጊኝ፡፡፲፮. ደስ ያላቸው የምእመናን ሁሉ መመከያቸው ፍሥሕት ድንግል ሆይ ለዘለዓለም በማያልቀው በልጅሽደስታ ደስ አሰኝኝ ያለ ርኩሰት የሠርግ ቤት የመንፈስ ቅዱስ ሙሽራ የመለኮት ዙፋን ድንግል ሆይ፡፡ልቡናዬን ከምታረክሰው ነፍሴንም ከምትጠብሳት ከሥጋ ፈቃድ ንጹሕ አድርጊኝ፡፡፲፯. እንደ ባሕር ከጠለቀው ርኩስ ሣቅ ጨዋታ ከክፉውም ከሴሰኝነት ማዕበል ሞገድ የምታሻግር የወርቅመሰላል ድንግል ሆይ ከዕዳ በደል ረግረግ አሻግሪኝ፡፡፲፰. ኖኅ ከማየ አይኅ ረግረግ የዳነባት መርከብ ድንግል ሆይ የሰው ሁሉ ልጆች ከሚመጣው መቅሠፍረግረግ የዳነባት መርከብ ድንግል ሆይ የሰው ሁሉ ልጆች ከሚመጣው መቅሠፍትፈግረግ አውጭኝ በኃጢአት እንደኔ የረከሰ ሰው የለምና ዘፍጥረት ፯፣ ፳፫፡፡፲፱. በጎ ሥራዬም ሁሉ እንደ ግዳጅ ጨርቅ ነው፡፡ ርኩሰቴም ደግሞ ከደመ ሕርስ ሁሉ እጽፍ ድርብእንደሚሆን የወለደች ሴት ርኩሰት ሁና እንደምትሰነብት እንደ ሰባቱ ቀር ርኩሰት ያለ ነው፡፡፳. ለመንጻቴ ማንን እጠራለሁ፡፡ ቁስሌንስ ለመፈወስ ወደ ማን እጮሃለሁ የኃጥአን ዕዳ በደላቸውንጹሕ መሆና የቁስለኞችም የቁስላቸው መፈወሻ ከምትሆን ካንቺ ሌላ፡፡፳፩. ከልጅሽ ሌላ ባለመድኃኒት አልሻም፡፡ ከጸሎትሽም ረዳትነት በቀር ደግሞ ኃጢአቴንየሚያስተሠረይልኝ አልፈልግም፡፡ ንጽሕት ሆይ ከርኩሰቴም ከዕዳም በደሌም ሁሉ ንጹሕ አድርጊኝ፡፡ከሥጋና ከነፍስ ቁስሌም ፈውሽኝ፡፡፳፪. ለደዌ መድኃኒት ይሹለታል ለቁስልም አቃቄር መልካሙን ቅመም ይፈልጉለታል የኃጢአት ቁስልግን ያለ ልጅሽ ፈቃድ አይጠግም፡፡

No comments:

Post a Comment