13

.

"በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው::" የማቴዎስ ወንጌል 7: 4

"እናንተ የተጠማችሁ ሁሉ፥ ወደ ውኃ ኑ፥ ገንዘብም የሌላችሁኑና ግዙ ብሉም ኑ ያለ ገንዘብም ያለ ዋጋም የወይን ጠጅናወተት ግዙ።" ትንቢተ ኢሳይያስ 55 : 1

Thursday, March 6, 2014

"ሁሉን የምትገዛ ጌታ አምላክ ሆይ፥ ሥራህ ታላቅና ድንቅ ነው" ቅ.ዮሐንስ ራእይ ም 15፡3-4


በሻሌ ንቡ ቅ/ሚካኤል ቅ/እስጢፋኖስ  ወአባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ቤተክርስቲያን


አሁን አገልግሎት እየሰጠ ያለው ቤተክርስቲያን











ከቤተመቅደሱ የተቆረጠው ማር ህዳር 12 ቀን 2006 ዓ.ም የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል ሲከበር ለሕዝበ ክርስቲያኑ በታየበት ወቅት






ታላቁ ጻድቅ አቡነ ሠላማ ከሣቴ ብርሃን



ሕዳር 11 ቀን 2002 ዓ.ም የቅዱስ ሚካኤል ዋዜማ ወደ ቤተመቅደስ ገብቶ መንበሩ ላይ የሚገኘው የንብ መንጋ




ከቤተመቅደሱ የተቆረጠው የማር እንጀራ ለሕዝበ ክርስቲያኑ በታየበት ወቅት




ታሕሣሥ 9 ቀን 2004 ዓ.ም መጥቶ ወደ ግብር ቤት ገብቶ ሰፍሮ የሚገኘው የንብ መንጋ በከፊል






ታሕሣሥ 19 ቀን 2005 ዓ.ም መጥቶ ወደ ቤተመቅደሱ  ገብቶ 
በአጎበሩ

 ላይ 
ሰፍሮ የሚገኘው የንብ መንጋ በከፊል









ከቤተመቅደሱ የተቆረጠው የማር እንጀራ ለሕዝበ ክርስቲያኑ በታየበት  ወቅት



ከቤተመቅደሱ የተቆረጠው ማር ህዳር 12 ቀን 2006 ዓ.ም የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል ሲከበር ለሕዝበ ክርስቲያኑ በታየበት ወቅት 



 ተዓምረኛው በሻሌ ንቡ ቅ/ሚካኤል ቤተክርስቲያን
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

“የእግዚአብሔርን ሥራ በምድር ያደረገውን ታምራት እንድታዩ ኑ” መዝ. 45፡8
በንብ መንጋ የተከበበው የበሻሌ (ንቡ) ቅ/ሚካኤል፣ ቅ/እስጢፋኖስ እና ወአባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ቤተክርስቲያን አመሰራረትና ገቢረ ተዓምራት አጭር መግለጫ

ቤተክርስቲያኑ ከመመስረቱ በፊት በቦታው ላይ ሲከናወኑ የነበሩ ልዩ ልዩ ታምራት፡-
  1. ለብዙ ዓመታት ከተለያየ ቦታ ተጣልተው የነበሩ ምዕመናን ቦታው ላይ እየመጡ እርቀ ሰላም ሲፈጽሙበት ኖረዋል፤
  2.  ቤተክርስቲያኑ ከተተከለበት ቦታ ትልቅ የጽድ ዛፍ ላይ የሚወጣው ሙጫ እንደ እጣን ጢስ ሽታ ለብዙ ዓመታት አካባቢውን መዓዛው (ሽታው) ያውድ ነበር፡፡
  3. በዚሁ ቦታ ላይ  ሌሊት ሌሊት  የመላዕክት ዝማሬ (ጣዕመ ዜማ) የከበሮ ድምጽ ይሰማ እንደነበረ በዕድሜ የገፉ የአካባቢው አዛውንቶች ተናግረዋል፡፡
  4. በአካባቢው ከሚኖሩ ምዕመናን መካከል በመልካም ስራቸው የታወቁና ከ90 ዓመት በላይ ዕድሜ የነበራቸው እናት የቅዱስ ሚካኤል ታቦት (ጽላት) እንደሚተከል በተደጋጋሚ ለሕዝበ ክርስቲያኑ ይናገሩ ነበር፡፡
  5.  ቀደም ሲል በእነ አብርሃ ወአጽብሃ ዘመነ መንግሥት አካባቢ ጀምሮ ከተለያየ አካባቢ የሞቱ አባቶች አስከሬናቸው እየመጣ ሥርዓተ ቀብር ሲፈጸምበት የቆየ እና በተለያየ ጊዜ የቀስተ ደመና ብርሃን በመቃብሩ ላይ ይታይ እንደነበር በአካባቢው የሚኖሩ በዕድሜ የገፉ አዛውንቶች በግልጽ መስክረዋል፡፡ ዛሬም መቃብሩ በግልጽ ይታያል፡፡ ይህ ሁሉ ታሪክ ሲከናወን ከቆየ በኋላ እግዚአብሔር የፈቀደው ጊዜ ሲደርስ በአካባቢው ከሚኖሩ በዕድሜ ከገፉ አዛውንቶች መካከል በአንድ አርሶ አደር ምዕመን አማካኝነት በእግዚአብሔር ፈቃድ በተደጋጋሚ  ራዕይ ተገልጾላቸው ያርሱበት የነበረውን ይዞታቸውን መሬት ለዚህ ታቦት መትከያ ቤተክርስቲያን እንዲሰራ መሬት በመስጠት አሁን በሚገኘው መቃኞ ቤተክርስቲያን ግንቦት 12 ቀን 2001 ዓ.ም ታቦቱ ሊገባ ችሏል፡፡
በቤተመቅደሱ ስለሚገኘው የንብ መንጋ አገባብ (አመጣጥ)
እግዚአብሔር አስቀድሞ ቦታውን ስለመረጠው፡-
1. ሕዳር 12 ቀን 2002 ዓ.ም የቅዱስ ሚካኤል በዓል ሲከበር በዋዜማው ሊቃውንቱ በአገልግሎት ላይ እንዳሉ ማለትም ሕዳር 11 ቀን 2002 ዓ.ም ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ገደማ ከምስራቅ አቅጣጫ የንብ መንጋ መጥቶ የቃል ኪዳኑ ታቦት በሚገኝበት በመንበሩ ውስጥ ገብቶ ካደረ በኋላ በነጋታው ታቦቱ ወጥቶ በሚከበረበት ጊዜ ንቡ ከመንበሩ ወጥቶ እንደ ደመና ረቦ ካሉት ምዕመናን ጋር ታቦቱን ዙሮ አክብሯል፡፡ በዕለቱም ይህን አስደናቂ ታምር ያዩና የተመለከቱ ምዕመናንም በከፍተኛ ድምጽ እግዚአብሔርን አመስግነዋል፡፡
2. ሕዳር 11 ቀን 2004 ዓ.ም የድንግል ማርያም ዕለት ካህናቱ ቅዳሴ ገብተው በሚቀድሱበት ጊዜ ቅዱስ ወንጌል ሲነበብ የንብ መንጋ መጥቶ ከቤተክርስቲያኑ ጉልላት ላይ የመስቀል ምልክት ሰርቶ ከሰፈረ በኋላ ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ላይ ተነስቶ ቤተክርስቲያኑን ዙሮ ወደ ቤተልሔም ውስጥ ገብቶ እስከአሁን ድረስ ሰፍሮ ይገኛል፡፡
3. ታህሳስ 9 ቀን 2004 ዓ.ም ከቀኑ 9፡00 ሰዓት የንብ መንጋ መጥቶ ከቤተክርስቲያኑ ጎን ላይ ከሰፈረ በኋላ ከቀኑ 11፡30 ተነስቶ ቤተክርስቲያኑን ዙሮ ወደ ግብር ቤት ገብቶ እስከአሁን ድረስ ሰፍሮ ይገኛል፡፡
4. ታህሳስ 19 ቀን 2005 ዓ.ም የቅዱስ ገብርኤል ዕለት ካህናት ቅዳሴ ገብተው በሚቀድሱበት ጊዜ ቅዱስ ወንጌል ሲነበብ የንብ መንጋ መጥቶ በሴቶች መግቢያ በር ወደቤተክርስቲያኑ ከገባ በኋላ በቀጥታ ወደ ቤተመቅደሱ ውስጥ ገብቶ  በአጎበሩ ላይ ሰፍሯል፡፡ ይህ በቤተክርስቲያናችን ላይ ያለው የንብ መንጋ ማሩ ተቆርጦ በተለያየ ጊዜ ለሕዝበ ክርስቲያኑ ተሰጥቶ ከአገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ በጉበት፣ በካንሰር፣ በኪንታሮት፣ በስኳር፣ በአስም፣ በጨጓራ፣ በኩላሊት፣ በደም ግፊት፣ በኤች አይ ቪ፣ ሽባዎች፣ አይነስውራን፣ አፈ ዲዳዎወች፣ መስማት የተሳናቸው፣ በጭንቀትና በልዩ ልዩ በሽታ የታመሙ ሰዎች ማሩን በልተው ጸበሉን ጠጥተው እምነቱን ተቀብተው ከበሽታቸው ተፈውሰው ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡ እንዲሁም ለብዙ ዓመታት ልጅ አጥተው የነበሩ ሰዎች (መካኖች) በአንድ ጊዜ ሁለት ልጆች መንታ እንዲሁም በአንድ ጊዜ ሶስት ልጆች መንታ ወልደው ታቅፈው መጥተው ጥምቀተ ክርስትናቸውን በዚሁ ቤተክርስቲያን እንዲፈፀም ማድረጋቸውና ሌሎች በዚህ አነስተኛ ጽሁፍ ሊገለፁ የማይችሉ በርካታ ገቢረ ታምራትና ፈውሶች እስከአሁኗ ሰዓት እየተደረጉ ናቸው፡፡  ክብርና ምስጋና ለአምላካችን ለልዑል እግዚአብሔር ይሁን አሜን፡፡
በእግዚአብሔር ፈቃድ በንቦቹ የተደረገው ታምራት በከፊል
1.  ሕዳር 12 ቀን 2002 ዓ.ም የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል ታቦቱ ወጥቶ በሚከበርበት ጊዜ ከቤተመቅደሱ ያለው ንብ ወጥቶ ታቦቱን አክብሯል፡፡
2.  የ2003 ዓ.ም የስቅለት በዓል ሲከበር ንሴብሆ እየተባለ በሚዘምርበት ጊዜ ንቡ ወጥቶ ቤተክርስቲያኑን ዙሮ ገብቷል፡፡
3.  መጋቢት 12 ቀን 2004 ዓ.ም የቅዱስ ሚካኤል ወርሃዊ በዓል ቅዳሴ እየተቀደሰ ሳለ የቤተመቅደሱ ንብ ከመንበሩ ላይ የመስቀል ምልክት ሰርቶ (ሰፍሮ) ታይቷል፡፡
4.  ሕዳር 11 ቀን  2005 ዓ.ም ንቡ ለመጀመሪያ ጊዜ የገባበትን ዕለት ለማስታወስ ከቀኑ 4፡00 ሰዓት ላይ ንቡ ወጥቶ ቤተክርስቲያኑን ዙሮ ገብቷል፡፡
5.  የ2005 ዓ.ም ፀሎተ ሐሙስ የሕጽበተ እግር ጸሎት ሲከናወን የመቅደሱ ንብ ወጥቶ ፀበሉ ላይ ሰፍሮ (ረቦ) ታይቷል፡፡ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይገባል፡፡ ለዘላለሙ አሜን፡፡

በቤተክርስቲያኑ ላይ የቃል ኪዳኑ ታቦት የሚነግስበት ቀናት
1. ሕዳር 12፣ ጥር 12፣ ግንቦት 12 ቅዳሴ ቤቱ፣ ሰኔ 12 ቀን የመልዓኩ የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በየዓመቱ ታቦቱ ወጥቶ ይነግሳል፡፡
2. ጥቅምት 17 እና ጥር 1 ቀን የሰማዕቱ የቅዱስ እስጢፋኖስ ዓመታዊ በዓል ታቦቱ ወጥቶ ይነግሳል፡፡
3. ታሕሳስ 18 እና ሐምሌ 26 ቀን የጻድቁ አቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ዓመታዊ በዓል ታቦቱ ወጥቶ ይነግሳል፡፡ በእነዚህ የንግስ በዓላት ላይ ከቤተመቅደሱ የተቆረጠው ማር ለመድኃኒትነት ይሰጣል፡፡
የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት፣ የቅዱስ እስጢፋኖስ እና የጻድቁ አቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን አማላጅነት ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን ፡፡
በ2006 ዓ.ም በቤተክርስቲያኑ አውደ ምህረት ላይ የሚደረጉ መንፈሳዊ ጉባዔያት
1ኛ. የካቲት 30 ቀን 2006 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00-5፡00 ሰዓት ጉባኤው ይካሄዳል፡፡
2ኛ. መጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00- 5፡00 ሰዓት ጉባኤው ይካሄዳል፡፡
3ኛ. ጳጉሜን 2 ቀን 2006 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00- 5፡00 ሰዓት ጉባኤው ይካሄዳል፡፡ በእነዚህ ጉባኤ ላይ ለመድኃኒነትነት ማር ይሰጣል፣
አድራሻ፡- በአዲስ አበባ በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 10 የሚገኝ ሲሆን ከተለያየ አቅጣጫ ተነስተው መገናኛ ከመገናኛ ሲኤም ሲ መሪ አያት የሚለውን ትራንስፖርት ይዘው አያት አደባባይ ይውረዱ፡፡ ከአያት አደባባይ ባጃጆች እና ታክሲዎች በሻሌ ንቡ ሚካኤል እና እስጢፋኖስ ካሉ እስከቤተክርስቲያኑ ያደርሰዎታል፡፡
ለበለጠ መረጃ፡- 0911- 56 37 14/0913-14 80 07 ንቡ ሚካኤል ብለው ይደውሉ
ወደፊት የቤተክርስቲያኑን ታሪክ በሰፊው እናቀርባለን፡