13

.

"በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው::" የማቴዎስ ወንጌል 7: 4

"እናንተ የተጠማችሁ ሁሉ፥ ወደ ውኃ ኑ፥ ገንዘብም የሌላችሁኑና ግዙ ብሉም ኑ ያለ ገንዘብም ያለ ዋጋም የወይን ጠጅናወተት ግዙ።" ትንቢተ ኢሳይያስ 55 : 1

Wednesday, December 26, 2012

ታሕሳስ 19 - በዓሉ ለቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት


በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

ስንክሳር ዘታሕሳስ
ታሕሳስ 19 - በዓሉ ለቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት
ገብርኤል ማለት “እግዚእ ወገብር” ማለት ነው። በዕለተ እሑድ መላእክት “መኑ ፈጠረነ፡ ማን ፈጠረን” ሲሉ ዲያብሎስ እኔ ፈጠርኳችሁ ብሎ ፈጥሮ ለማሳየት እጁን ከእሳት ከትቶ አቃጥሎት መላእክት በተረበሹ ጊዜ “በያለንበጽ እንቁም” ብሎ ያረጋጋቸው መልአክ ነው። በዚኅም ምክንያጽ ጌታ “በእንተዝ ይደልዎ ከመይጹር ዜናሃ ለማርያም” እንዲል ሥጋዌውን ለድንግል እንዲያበስር አድሎታል። ከዚህም በኋላ ደጋግ ሰዎችን ለመርዳት የሚወጣ የሚወርድ ሆኗል።


በዚህም ዕለት አግብርተ - እግዚአብሔር አናንያ አዛርያ ሚሳኤልን ከእቶነ እሳት አድኗቸዋል። ይህስ እንደምን ነው? ቢሉ ተማርከው ፋርስ ባቢሎን ሲኖሩ ንጉሡ ናቡከደነጾር ዳንኤልን አራተኛ አድርጎ ጥበበ ባቢሎን ይማሩ ብሎ ከቤተ - መንግሥት  አስቀመጣቸው። መጋቢያቸው ሜልዳር ሥጋ በገበታ ጠጅ በዋንጫ አቀረበላቸው። “ይህንን አንበላም ጥቂት ጥሬ እና ጥሩ ውኃ ስጠን” አሉት። “ንጉሥ ከስታችሁ ቢያይ ይቆጣል” አላቸው። “ቀን ስጠን” ቢሉት ! ቀን ሰጣቸው። ጥሬ እየቆረጠሙ ውኃ እየጠጡ ሰንብተው ጮማ ከሚበሉት ጠጅ ከሚጠጡት ይልቅ አምረው ደምቀው ተገኙ። በዚሁ ሲማሩ ቆይተው ጌታ ጥበቡን ገልጾላቸው ጠቢባን ሲሆኑ ይልቁንም ዳንኤል ርእሱ ዘወርቅን ለንጉሱ ከተረጎመለት በኋላ በሦስት አውራጃዎች ሾማቸው። ባቢሎናውያን ቀንተው ለማጣላት ምክንያት ይሆነናል ብለው “ንጉሥ እንዳየኸው ምስል አድርገህ አሰርተህ አቁም ወዳጅ ጠላትህን በሱ ትለያለህ” አሉት። & ክንድ ቁመት፣ 6 ክንድ ስፋት ያለው የወርቅ ምስል አሰርቶ በአዱራን ሜዳ አቁሞ “ያልሰገደ ይቀጣል” ብሎ አዋጅ ነገረ። ሁሉ ሲሰግዱ ሠለስቱ ደቂቅ “አንሰግድም” አሉ። ሄደው ነገሩት። አስጠርቶ “አንሰግድም አላችሁን?” አላቸው። “አዎን” አሉት። “መኑ ያድኅነክሙ እምእዴየ፤ ማን ያድናችኋል?” አላቸው። “ሀሎነ አምላክነ ዘፈጠረ ኪያከ ወኪያነ፤ እኛንና አንተን የፈጠረ አምላካችን ያድነናል” አሉት። ነበልባሉ $9 ክንድ የሆነ እሳት አስነደደ።
ከዚህ በኋላ ኃያላኑን መርጦ የኋሊት አሳስሮ ከእሳቱ አስጣላቸው። እኒያን ወላፈኑ ገድሏቸዋል። እነርሱን ግን “ወወረደ መልአከ እግዚአብሔር ምስለ እለ አዛርያ ውስተ እቶን ወዘበጦ ለነበልባለ እሳት ወረሰዮ ከመ.ማይ ቆሪር ዘጊዜ.ጽባሕ” ይላል ቅዱስ ገብርኤል ወርዶ በዘንጉ ቢነካው ውኃ ሆኗል። ባቢሎናውያን የቀደመው  ሲጠፋ ጨማምረው አነደዱባቸው። 

እነርሱ ግን ምንም ሳይሆኑ “ይትባረክ እግዚአብሔር አምላከ አበዊነ፤ ስቡህኒ ውእቱ ወልዑልኒ ውእቱ ለዓለም። እያሉ ሲያመሰግኑ አድረዋል።
በጧት ናቡከደነጾር ከሰገነቱ ሆኖ ሲመለከት አራት ሆነው በእሳቱ ውስጥ ሲመላለሱ አይቶ “ትማልም አሢረነ ሠለስተ አደወ ወደደነ ውስተ.እቶነ.እሳት፤ ትናንት ሦስት ሰዎች አስረን ከእሳቱ እቶን ጥለን ነበር፤ ወዮምሰ እሬኢ አርባዕተ እደወ እንዚ ያንሶሰዉ ማዕከለ.እሳት ፍቱሐኒሆሙ፤ ዛሬ ግን አራት ሆነው ከእሥራታቸው ተፈትተው በእሳቱ ውስጥ ሲመላለሱ አያለሁ። ወራብዑለ ይምስል ከመ ወልደ.እግዚአብሔር፤ እንደውም አራተኛው የእግዚአብሔር ልጅ ይመስላል” አለ።ወዲያውም ከእቶኑ ሔዶ “አንትሙ ሲድራቅ ወሚሳቅ ወአብደናጎ አግብርተ.እግዚአብሔር ንዑ ፃዑ ዝየ፤ እናንተ ሲድራቅ ሚሳቅና አብደናጎ የእግዚአብሔር አገልጋዮች ኑ ውጡ።” አላቸው። ምንም ሳይሆኑ ወጥተዋል።በልብሳቸው ላይ ጥላት እንኳን አልተገኘም። ናቡከደነጾር ይህን አይቶ “ይትባረክ እግዚአብሔር አምላከ ሲድራቅ ወሚሳቅ ወአብደናጎ ዘፈነወ መልአኮ ወአድኀነ አግብርቲሁ፤ መልአኩን ልኮ ባለሟሎቹን ያዳነ የሲድራቅ የሚሳቅ የአብደናጎ አምላክ እግዚአብሔር ይመስገን።” አለ። “ንጉሥ እውነት መሰለህ በሥራያቸው ነው” አሉት ባቢሎናውያኑ። “በሥራይ ከሆነማ ከእናንተ የሚበልጥ የለም በሥራያችሁ ዳኑ” ብሎ ከእሳቱ ጨምሯቸው ተቃጥለዋል። ንጉሡም “ከሲድራቅ ከሚሳቅ ከአብደናጎ አምላክ ከእግዚአብሔር በቀር ማዳን የሚቻለው የለምና እሱን አምላኩ ብሎ አዋጁን በአዋጅ መልሶታል። እነሱንም በሹመት ላይ ሹመት በክብር ላይ ክብር ጨምሮላቸዋል። (ት.ዳን ም.3)
የሊቀ መልአኩ የቅዱስ ገብርኤል ጠባቂነቱ፣ አማላጅነቱ፣ ረድኤትና በረከቱ በሀገራችን በኢትዮጵያና በሕዝበ.ክርስቲያኑ ላይ ለዘለዓለም ይኑር። አሜን።

“ይትባረክ እግዚአብሔር አምላከ አበዊነ”

የቦ/መ/ብ/ቅ/እግዚአብሔር አብ ቤ/ክ ሰ/ት/ቤት
ወርሐ ታሕሳስ/@)5 ዓ.ም
www.holyfathersundayschool.blogspot.com
source:መዝገበ - ታሪክ 

1 comment: